በደቡብ ወሎ ዞን ተንታ ወረዳ በ01 በአምባ ማርያም ከተማ ለሚገኙ ተፈናቃዮች የአልባሳት ድጋፍ ተደረገ።

የአልባሳት ድጋፉ የተደረገው በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተንታ ወረዳ ተወካይ በሆኑት በአቶ ሀብተማርያም መኮነን አማካኝነት ከኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን የተሠበሠበ መሆኑ ተገልጿል።

በዕለቱ የተንታ ወረዳ ዋ/አስተዳዳሪ አቶ መሀመድ ሰይድና የተንታ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ አበበ አለባቸው በተገኙበት የአልባሳት ስርጭቱ ተከናውኗል።

በቀጣይም በሌሎች ተፈናቃይ ባሉባቸው ቦታዎች የአልባሳት ስርጭቱ ይከናወናል።

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Scroll to Top