





በደቡብ ጎንደር አስተዳደር ዞን እብናት ወረዳ የፌደራል አደጋ መከላከልና አመልድ ኢትዮጵያ የተፈጥሮ አደጋ ተጋላጭ ለሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች የምግብ እህል ድጋፍ እየተደረገ ነው።
በእብናት ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት የቅድመ ማስጠንቀቂያና ፈጣን ምላሽ ቡድን መሪ የሆኑት አቶ ደስታየ ከፍያለው እንደገለጹት በወረዳው የድርቅ ተጋላጭ ለሆኑ አስራ ሁለት ቀበሌዎች ከ79,000 በላይ የህ/ሰብ ክፍል የሁለት ወር ቀለብ የበቆሎና አልሚ ምግብ እህሎችን ድጋፍ እያደረግን ነው ሲሉ ገልጸዋል።
በተፈጥሮ አደጋ ተጋላጭ የሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎችም እየተደረገላቸው ላለው ድጋፍ አመስግነዋል።
